ዜና | Oduu | News
የቂርቆስ ክ/ከተማ መስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት የ6 ወር እቅድ አፈፃፀሙን ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ፡፡

በግምገማው ወቅት የጽ/ቤቱ ሃላፊ ወ/ሮ ፍፁም እንደገለፁት ባለፉት 6 ወራት በመስሪያ ቦታ አሰጣጥ ለበርካታ ሴቶች፤ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ በመስጠት ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ የውይይቱም ተሳታፊዎች በበኩላቸዉ እንደገለፁት ፅ/ቤቱ ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር አገልግሎቱን ማሻሻል መቻሉ እና በተቋም ደረጃ በቴክኖሎጂ ተደግፈው የሚሠጡ አገልግሎቶች የላቀ ውጤት መመዝገቡን በመግለፅ ቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል። በመጨረሻም በ6 ወሩ የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ አካላት እዉቅና ተሰጥቷል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ቂርቆስ ክ/ከተማ መስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት ባለሙያዎችና አመራሮች በ2017/18 በክረምት ወቅት የተተከሉ ችግኞችን ውሃ የማጠጣት እና ሌቾች የእንክብካቤ ስራዎችን አከናወኑ።

ቂርቆስ ክ/ከተማ መስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊ በችግኝ እንክብካቤ መርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የመተባበርና የአንድነት ውጤት ማሳያ መሆኑን ገልጸው የሚተከሉ ችግኞች የአየር ንብረት ለውጡን ከመከላከል ባሻገር ለከተማው ውበት የሚሰጡና ለምግብነት የሚውሉ በመሆናቸው መትከል ብቻውን ውጤት ባለመሆኑ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ የሁላችንም ሃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በስታንዳርድ አመዘጋገብ ዙሪያ ለባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ።

በቂርቆስ ክ/ከተማ መስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት በስታንዳርድ አመዘጋገብ ዙሪያ ለባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ወርቃማዋ ሰኞ ሳምንታዊ የሰራተኞች ማነቃቅያ ፕሮገራም ተካሄደ።

በቂርቆስ ክ/ከተማ መስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት በሳምንቱ ሁሉም አመራሮችና ሰራተኞች የሚሳተፉበት እጅግ አስተማሪ የሆነ የወርቃማ ሰኞ ፕሮግራም ተካሄደ። በማነቃቂያ መርሀ-ግብሩ ሁሉም የጽ/ ቤቱ ሰራተኞች ተገኝተውበታል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለ100 ኢንተርፕራይዞች እና ለ329 አንቀሳቃሾች የመስሪያ ቦታ ቁልፍ ርክክብ አካሄደ፡፡

ክፍለ ከተማው በዛሬው እለት የስራ እድል ለተፈጠረላቸው 100 የሚሆኑ ኢንተርፕራይዞችን እና በውስጣቸው የሚገኙ 329 አንቀሳቃሾችን ቁልፍ አስረክቧል። የእድሉ ተጠቃሚ ለሆኑት ዜጎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ምስክር ነጋሽ እንደተናገሩት መንግስት ለዜጎች ካለው የላቀ ክብር የስራ እድል በመፍጠር ብቁ ዜጋ እያፈራ ይገኛል ብለዋል። መንግስት ለዜጋው በተለይ ለስራ ፈላጊው ወገን ተቆርቁሮ የስራ እድል በመፍጠርና በማመቻቸት በሀገራችን ቀዳሚው የለውጥ አመራር ነው ያሉት ዶክተር ምስክር ከዚህም አኳያ ከሰባት አመት ወዲህ በየአመቱ በየክፍለ ከተማው፣ በየወረዳው፣ በየብሎኩ ያሉ የስራ እድል ያልተፈጠረላቸው ዜጎች በማኑፋክቸር፣ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎት፣ በከተማ ግብርና በተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ተቀጥረው እንዲሰሩ እንዲሁም በሁሉም ዘርፍ በመለየትና በመመዝገብ በቴክኒክ እና በልዩ ልዩ ስልጠናዎች ከቴክኒክና ሙያና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት ስልጠና በመስጠት በማብቃት ወደስራ ከመግባታቸው በፊት ግንዛቤ እንዲይዙ ማድረግ ቀጥሎ ደግሞ መስሪያ ቦታ እና ሼዶችን እንዲሁም የተለያዩ ኢንተርፕራይዞችን በማመቻቸት ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል፡፡ የተፈጠረላቹ የስራ እድል እናንተን፣ ቤተሰቦቻችንን ከመጥቀም አልፎ ለሀገር ጭምር የሚያበረክተው አሰተዋጽኦ ከፍተኛ ነው እናንተም ስራን ሳትንቁ ስራን አክብራቹ በተፈጠረላቹ የስራ እድል በመጠቀም የስራ እድል ላላገኙ ወገኖች ጭምር የስራ እድል ለመፍጠር በርትታቹ እንድትሰሩ ሲሉም መልእክታቸውን አስተላፈዋል፡፡ በክፍለ ከተማው 199 ብሎኮች አሉ፤በእነዚህ ብሎኮች ላይ ምርታማነትን ከመጨመር፣ ስራ ከመፍጠር አኳያ ለበርካታ ዜጎች በስራ እድል ፈጠራ ላይ የሰራንበት ሁኔታ ነው ያለው ያሉት ደግሞ በክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈጻሚና የስራ ክህሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘመን ተስፋዬ ናቸው። መስሪያ መሸጫ ቦታ መስጠት ብቻ አይደለም የእኛ ሀላፊነት በቅርበት መከታተል፣ የገበያ ትስስር መፍጠር፣ የክህሎት ክፍተት ካለም ሞልተን በተለይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠቃሚ ሁናችሁ በአካባቢያችሁ ኢኮኖሚ ላይ ተጽዕኖ እንድትፈጥሩ ለማድረግ ከጎናችሁ ነን ሲሉም አቶ ዘመን መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ጽ/ቤታችን በ6ወር አፈጻጸም ምዘና የላቀ አፈጻጸም በማምጣት ከ10 ክ/ከተሞ 2ኛ በመውጣት የእውቅና ሰርተፍኬት ማግኘት ችሏል፡፡

እንኳን ደስ ያለን ጽ/ቤታችን በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር የመስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ በ6ወር አፈጻጸም ምዘና የላቀ አፈጻጸም በማምጣት ከ10 ክ/ከተሞ 2ኛ በመውጣት የእውቅና ሰርተፍኬት ማግኘት ችሏል፡፡

image
image
image
image